ቀጥታ፡

የኢቢሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ አብዱራህማን ሩቤ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አዲስ አበባ ፤ታህሳስ 14/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እያገለገሉ የነበሩት አቶ አብዱራህማን ሩቤ ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል::

ባደረባቸው ሕመም ምክንያት በህክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት የአቶ አብዱራህማን ሥርዓተ ቀብር ዛሬ እንደሚፈጸም ተገልጿል።

አቶ አብዱራህማን ከሪፖርተርነት እስከ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚነት በተለያዩ የሚዲያ ተቋማት አገልግለዋል::

በተለይም በኦቢኤን እና በኢቢሲ ከሪፖርተርነት ጀምሮ በኃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል::

ህይወታቸው እስካለፈበት ቀን ድረስ ደግሞ የኢቢሲ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው እያገለገሉ ነበር::

አቶ አብዱራህማን ባለትዳር እና የሦስት ልጆች አባት ነበሩ::

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አብዱራህማን ሩቤ ህልፈት የተሰማውን ሃዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቻቸው ለወዳጆቻቸው እና ለሥራ ባልደረቦቻቸው መፅናናትን ይመኛል::

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም