ቀጥታ፡

ፍትህ ወልደሰንበት (ዶ/ር)  የአፍሪካ እጅ ኳስ ኮንፌዴሬሽን ዞን አምስት ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ 

አዲስ አበባ፤ታህሳስ 11/2018(ኢዜአ):- የኢትዮጵያ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ፍትህ ወልደሰንበት (ዶ/ር) የአፍሪካ እጅ ኳስ ኮንፌዴሬሽን ዞን አምስት ፕሬዝዳንት ሆነው በድጋሚ ተመርጠዋል። 

የአፍሪካ እጅ ኳስ ኮንፌዴሬሽን ዞን አምስት ስብስባ በግብጽ ካይሮ ተካሄዷል። 

በስብሰባው ላይ የዞን አምስት አባል ሀገራት ፍትህ ወልደሰንበት (ዶ/ር)  የአፍሪካ እጅ ኳስ ኮንፌዴሬሽን ዞን አምስት ፕሬዝዳንት  እንዲሆኑ በድጋሚ መርጠዋቸዋል። 

ፍትህ ወልደሰንበት (ዶ/ር) የአባል ሀገራቱን ሙሉ ድጋፍ ማግኘታቸውን የኢትዮጵያ እጅ ኳስ ፌዴሬሽን መረጃ ያመለክታል።

ፕሬዝዳንቱ ፌዴሬሽኑን ለቀጣይ አራት ዓመታት ይመራሉ። 

ፍትህ ወልደሰንበት (ዶ/ር) እ.አ.አ 2021 አንስቶ ኮንፌዴሬሽኑን በፕሬዝዳንት እያገለገሉ ይገኛል። 

ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ብሩንዲ፣ ጅቡቲ፣ ሩዋንዳ፣ ታንዛንያ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ዩጋንዳ፣ ሶማሊያ እና ግብጽ የአፍሪካ እጅ ኳስ ኮንፌዴሬሽን ዞን አምስት አባል ሀገራት ናቸው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም