ቀጥታ፡

የኢትዮጵያ እና ህንድ የረጅም ጊዜ ታሪካዊ ግንኙነት ተጠናክሮ ይቀጥላል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) 

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 8/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ እና ህንድ የረጅም ጊዜ ታሪካዊ የሁለትዮሽ ትብብር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ኢትዮጵያን ዳግም እንደሚጎበኙ ተስፋ አለኝ ብለዋል።


 

ኢትዮጵያ እና ህንድ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ዲፕማሲያዊ ግንኙነት በዘላቂነት ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም