ቀጥታ፡

ምክር ቤቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ነው

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 3/2018(ኢዜአ)፦የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከክልል የፖለቲካ የጋራ ምክር ቤቶች ጋር የምክክር መድረክ እያካሄደ ነው።

በመድረኩ የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የክልል የጋራ ምክር ቤቶች የ2017 ዓመታዊ ሪፖርት እና የ2018 ዕቅድ ማዕቀፍ ቀርቦ ውይይት እንደሚካሄድበት ተገልጿል።

የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ሰብሳቢ አቶ ሰለሞን አየለ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ ምክር ቤቱ በሀገሪቱ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታን ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል።

ምክር ቤቱ ሀገራዊ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑንም ጠቅሰዋል።

ሀገራዊ ምክክሩ ስኬታማ እንዲሆን አጀንዳ አሰባስቦ ከማቅረብ ጀምሮ ከኮሚሽኑ ጋር በቅርበት እየሰራ እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ገለልተኛና ግልጽ እንዲሆን ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በጋራ እየሰራ መሆኑንም አመላክተዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም