ቀጥታ፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) “በመደመር መንግሥት ዕይታ የዘርፎች እመርታ” በሚል ርዕስ ለብልጽግና ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ስልጠና ሰጥተዋል። በክፍል ሁለት ካነሷቸው ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል…

 

🖍 የሀገራዊ ብልጽግና አእማዶች የተባሉት ኢኮኖሚ (ከሁሉም ለሁሉም በሁሉም)፣ ፖለቲካ (አካታችና አሳታፊ) እና ማኅበራዊ (ትውልዳዊ ልማት) ናቸው።

🖍 በችግር ትብታብ ታስረን እንዳንቀር ተስፈንጥረን ወደምንፈልገው ነገር እንድንደርስ በአንዳንድ ጉዳይ ላይ መደመራዊ ዝላይ አስፈላጊ ነው።

🖍 መደመራዊ የዝላይ መንገድ ዋና ዋና ዓላማዎች ከቀዳሚው ጋር ያለ ልዩነትን በፍጥነት ማጥበብ እና እመርታዊ እድገት ማምጣት ናቸው።

🖍 የትውልድ ግንባታ ስትራቴጂዎች የሚባሉት በጎ ፈቃድ አገልግሎት፣ ዲጂታል ዓርበኝነት፣ የትምህርት ተሃድሶ እና የባህል ኢንዱስትሪ ናቸው።

🖍 ማስተካከል፣ ማስፋፋት እና ማበርከት የመደመር ትውልድ መርሆዎች ናቸው።

🖍 የመደመር መንግሥት እንቅፋት - ሐሳብ አልቦነት ነው። ሐሳብ አልቦነት ማለትም በሕዝበኝነት መታወር እና መስከር፤ በነባር ባህል መታጠርና መታሰር ፤ በጊዜያዊ ችግር መሸበርና መሰበር ማለት ነው።

🖍 የሐሳብ ሉዓላዊነት- የመደመር አሸናፊነት ነው።በዚህም መሠረት አመክኗዊ ውይይትና ሙግት፣ ሚዛናዊ ትብብርና ፉክክር፣ ሐሳብን በወረቀት - ሥራን በመሬት መሆን አለበት።

🖍 ፍሪሊዮን - የመደመር ቀመር ነው። ይህ ማለትም መስጠትና አገልግሎት፣ ሰውን ማትረፍና ማብቃት፣ ወደ ሰላምና ብልጽግና፣ ስለ ሀገርና ትውልድ እንዲሁም ሐሳብና ሰው በተቋም ማለት ነው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም