ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ተወያዩ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ) ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፤ የኢትዮጵያ እና ፈረንሳይ ግንኙነት እየተከናወኑ ባሉ ትብብሮች መጠናከሩን ገልጸዋል።
በዚህ ረገድም ከፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ጋር ትብብሮቹ ስላሉበት ደረጃ መወያየታቸውን አመልክተዋል።