ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ ጋር ተወያዩ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ) ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከአውሮፓ ኅብረት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት አንቶኒዮ ኮስታ ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት የሁለትዮሽ ውይይቱ የኢትዮ-አውሮፓ ኅብረት ግንኙነት የማላቅ አላማ እንዳለው ገልጸዋል።
በውይይቱ በተለያዩ ዘርፎች ትብብራችንን የበለጠ ለማጠናከር አቋማችንን እንደገና አጽንተናል ሲሉም ገልጸዋል።