ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ፕሬዝዳንት ክሪስታሊና ጂኦርጂየቫ ጋር ተወያዩ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት ፕሬዝዳንት ክሪስታሊና ጂኦርጂየቫ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት(IMF) ፕሬዝዳንት ክሪስታሊና ጂኦርጂየቫ ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፤ ከቡድን 20 ጉባኤ ጎን ለጎን ከአይ.ኤም.ኤፍ ፕሬዝዳንት ክሪስታሊና ጂኦርጂየቫ ጋር በአለም አቀፍ የኢኮኖሚ አዝማሚያዎች ፣ በኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ሪፎርም እንዲሁም ዘላቂ እና አካታች እድገትን ለመደገፍ ትብብርን ለማጠናከር ያሉ እድሎች ላይ መወያየታቸውን ገልጸዋል።
ለአይ.ኤም.ኤፍ የዘለቀ ግንኙነት ምስጋናቸውን ያቀረቡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የጋራ ትኩረቶቻችንን ለመፈፀም መነሳታችንን እገልጻለሁ ብለዋል።