ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ጋር ተወያዩ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ጋር ተወያዩ
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 13/2018 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ጋር ተወያይተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት በቡድን 20 አባል ሀገራት የመሪዎች ጉባኤ ዋዜማ የአዘጋጇን ሀገር ደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ጋር መገናኘታቸውን ገልጸዋል።
ታሪካዊው የጂ-20 ጉባኤ በአፍሪካ ምድር እንደመሰናዳቱ በተለያዩ ጉዳዮች እንዲሁም በጉባኤው የአፍሪካ የወል ድምጽ እና የጋራ ፍላጎት የሚቀርብበትን ሁኔታ ላይ መወያየታቸውን አመልክተዋል።