የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንድን ነው? - ኢዜአ አማርኛ
የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንድን ነው?
• የማርበርግ ቫይረስ በሽታ በወረርሽኝ መልክ የሚከሰት የደም መፍሰስና ትኩሳት ህመም ነው።
• በሰዎችም ሆነ በሌሎች እንስሳት ላይ ይከሰታል።
የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምልክቶች ምንድን ናቸው?
ከአፍ፣ ከአፍንጫ ወይም ከቆዳ ሥር ደም መፍሰስ፤
ከፍተኛ ትኩሳት፣ ብርድ ብርድ ማለት እና ራስ ምታት፤
የጡንቻ እና ጀርባ ህመም፤
ማቅለሽለሽ፣ የሆድ ህመም እና ተቅማጥ፤
ደረት፣ ጀርባ እና ሆድ ላይ በጣም ጎልቶ የሚታይ ሽፍታ፤
ለቫይረሱ ከተጋለጡ ከሁለት እስከ ዘጠኝ ቀናት ውስጥ የበሽታው ምልክቶች ይታያሉ።
የማርበርግ ቫይረስ በሽታ መተላለፊያ መንገዶች ምንድን ናቸው?
• በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ደም፣ ሽንት፣ እንባ እና ሌሎች ፈሳሾች ጋር የሚፈጠር ቀጥተኛ ንክኪ፤
• በታመመ ወይም በሞተ ሰው የሰውነት ፈሳሽ የተበከሉ ቁሶች፣ እንደ ልብስ፣ አልጋ ልብስ፣ መርፌና ሌሎች መገልገያዎች ጋር በሚኖር ንክኪ፤
• በበሽታው ከተያዙ የሌሊት ወፎች ወደ ሰዎች ይተላለፋል።