ይርጋጨፌ ቡና በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ድል ቀንቶታል - ኢዜአ አማርኛ
ይርጋጨፌ ቡና በሴቶች ፕሪሚየር ሊግ ድል ቀንቶታል
አዲስ አበባ፤ ሕዳር 11/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪሚየር ሊግ የሰባተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ይርጋጨፌ ቡና ባህር ዳር ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል።
በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ በሬዱ በቀለ በስምንተኛው ደቂቃ የማሸነፊያውን ጎል አስቆጥራለች።
ሸገር ከተማ ከሊጉ መሪ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በአሁኑ ሰዓት በአበበ ቢቂላ መታሰቢያ ስታዲየም ጨዋታቸውን እያደረጉ ይገኛል።