የማርበርግ ቫይረስ መተላለፊያ መንገዶች እና መከላከያ ዘዴዎች - ኢዜአ አማርኛ
የማርበርግ ቫይረስ መተላለፊያ መንገዶች እና መከላከያ ዘዴዎች
የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምንድን ነው?
o የማርበርግ ቫይረስ በወረርሽኝ መልክ የሚከሰት የደም መፍሰስና ትኩሳት ህመም ነው።
o በሰዎችም ሆነ በሌሎች እንስሳት ላይ ይከሰታል።
የማርበርግ ቫይረስ በሽታ ምልክቶች ምንድን ናቸው?
ከአፍ፣ ከአፍንጫ ወይም ከቆዳ ሥር ደም መፍሰስ፤
ከፍተኛ ትኩሳት፣ ብርድ ብርድ ማለት እና ራስ ምታት፤
የጡንቻ እና ጀርባ ህመም፤
ማቅለሽለሽ፣ የሆድ ህመም እና ተቅማጥ፤
ደረት፣ ጀርባ እና ሆድ ላይ በጣም ጎልቶ የሚታይ ሽፍታ፤
ለቫይረሱ ከተጋለጡ ከሁለት እስከ ዘጠኝ ቀናት ውስጥ የበሽታው ምልክቶች ይታያሉ።
የማርበርግ ቫይረስ መተላለፊያ መንገዶች ምንድን ናቸው?
• በቫይረሱ ከተያዘ ሰው ደም፣ ሽንት፣ እንባ እና ሌሎች ፈሳሾች ጋር የሚፈጠር ቀጥተኛ ግንኙነት፤
• በታመመ ወይም በሞተ ሰው የሰውነት ፈሳሽ የተበከሉ ቁሶች፣ እንደ ልብስ፣ አልጋ ልብስ፣ መርፌና ሌሎች መገልገያዎች ጋር በሚኖር ንክኪ፤
• በቫይረሱ ከተያዙ የሌሊት ወፎች ወደ ሰዎች ይተላለፋል።
የማርበርግ ቫይረስ በሽታ መከላከያ መንገዶች ምንድን ናቸው?
o ከላይ የተዘረዘሩት ምልክቶች ሲኖሩ ወደ ሕክምና ተቋም መሄድ፤
o ከታመመ ሰው ጋር ንክኪና ትኩሳት ካለ በአፋጣኝ ወደ ሕክምና ተቋማት መሄድ፤
o ሞት በሚከሰትበት ወቅት አስከሬኑን በባለሙያ ማዘጋጀትና መቅበር፤ አላስፈላጊ ቀብር ሥነ-ሥርዓቶችን ማስቀረት እና ንክኪ ያላቸውን ቁሶች ማስወገድ።
o ከታመመ ሰው ደምና ፈሳሽ ንክኪ ራስን መጠበቅ፤
o ለታመመ ሰው እንክብካቤ በምናደርግበት ጊዜ የመከላከያ ዘዴዎችን ማለትም የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ማስክ እና የእንጅ ጓንት መጠቀም።
o እጅን በሳኒታይዘር ወይም በሳሙናና በውኃ በአግባቡ መታጠብ።