በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አራት ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ - ኢዜአ አማርኛ
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ አራት ጨዋታዎች ዛሬ ይካሄዳሉ
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 15/2018 (ኢዜአ):- የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የዘጠነኛ ሳምንት መርሃ ግብር ዛሬ ሁለተኛ ቀኑን ይዟል።
ቼልሲ ከሰንደርላንድ እና ኒውካስትል ዩናይትድ ከፉልሃም በተመሳሳይ ከቀኑ 11 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።
ምሽት 1 ሰዓት ከ30 ላይ ማንችስተር ዩናይትድ በኦልድራፎርድ ስታዲየም ብራይተንን ያስተናግዳል።
ዩናይትድ በሩበን አሞሪም ስር በሊጉ ለመጀመሪያ ጊዜ ሶስተኛ ተከታታይ ድሉን ለማግኘት ይጫወታል።
ብሬንትፎርድ ከሊቨርፑል ምሽት 4 ሰዓት በጂቴክ ኮሙኒቲ ስታዲየም ይጫወታሉ።
የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ሊቨርፑል ከሶስት ተከታታይ ሽንፈቶች በኋላ ወደ አሸናፊነት እና ወደ ዋንጫ ፉክክር ለመመለስ የዛሬው ሶስት ነጥብ በእጅጉ ይፈልገዋል።