ቀጥታ፡

የጎንደር አብያተ መንግሥታት እድሳት የጎንደር ከተማን ወደ ሕይወት መልሷቷል - ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 14/2018(ኢዜአ)፡- የጎንደር አብያተ መንግሥታት እድሳት የጎንደር ከተማን ወደ ሕይወት መልሷቷል ሲሉ ፕሬዚዳንት ታየ አጽቀ ሥላሴ ገለጹ።

ፕሬዚዳንቱ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት የታሪካዊ ሥነ-ሕንፃዎች ጥበቃ እና እድሳት የሥነ-ሕንፃ እሴቶችን ለመጠበቅ ወሳኝ ነው ብለዋል።

ታላቅ የኢትዮጵያ ቤተ-መንግሥት የነበረው የጎንደር አብያተ መንግሥት በሚያምር እና የመነሻውን አርክቴክቸር በጠበቀ መልኩ ውብ ሆኖ መታደሱንም ገልጸዋል።

አሁን ጎንደር ድሮ እና ዘንድሮን አጣምራ የያዘች ማራኪ እና የምታምር ከተማ መሆኗን ነው ፕሬዚዳንቱ የጠቀሱት።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም