ድሬዳዋ ከተማ የሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል - ኢዜአ አማርኛ
ድሬዳዋ ከተማ የሊጉ የመጀመሪያ ድሉን አሳክቷል
አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 13/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሁለተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ወላይታ ድቻን 1 ለ 0 አሸንፏል።
ማምሻውን በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አቤል ነጋሽ በ76ኛው ደቂቃ የማሸነፊያ ግቧን አስቆጥሯል።
ድሬዳዋ ከተማ በሊጉ የመጀመሪያው ሶስት ነጥቡን አግኝቷል።
በአንጻሩ ወላይታ ድቻ በሊጉ ሁለተኛ ሽንፈቱን አስተናግዷል።