ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ - ኢዜአ አማርኛ
ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገለጹ

አዲስ አበባ ፤ጥቅምት 9 / 2018 (ኢዜአ) ፦ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሕልፈት የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል።
ፕሬዚዳንቱ ባስተላለፉት የሐዘን መግለጫ፤ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዚዳንት በነበሩት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ እረፍት በጥልቅ አዝኛለሁ ብለዋል፡፡
ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በመልካም አበርክቷቸው ሁሌም የሚታወሱ ናቸው ሲሉም ገልጸዋል፡፡
ፕሬዚዳንቱ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው ኢትዮጵያውያን መፅናናትን ተመኝተዋል፡፡
#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ