ቀጥታ፡

የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት የከንቲባ ተክሌ ጆንባን ሹመት አፀደቀ

‎ሀዋሳ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የከተማዋን ከንቲባ ተክሌ ጆንባን ሹመት አጽድቋል።

‎የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል።

‎ምክር ቤቱ በጉባኤው የቀረበለትን የከተማዋን ከንቲባ ተክሌ ጆንባን ሹመት ተቀብሎ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።


 

‎አቶ ተክሌ ጆንባ ከወረዳ እስከ ክልል በተለያዩ የሥራ ዘርፎች በኃላፊነት ሲመሩ መቆየታቸውም በወቅቱ ተጠቅሷል።


 

‎አዲሱ ከንቲባ ተክሌ ጆንባ በጉባኤው ፊት የተሰጣቸውን የህዝብና የመንግስት ኃላፊነት በታማኝነትና በቅንነት ለመወጣት ቃለ መሀላ የፈፀሙ ሲሆን ከቀድሞው ከንቲባ መኩሪያ ማርሻዬ የኃላፊነት ርክክብ አድርገዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም