ቀጥታ፡

በጋምቤላ ክልል ብሔራዊ ክብርና አርማ የሆነው የሰንደቅ ዓላማ ቀን በድምቀት ይከበራል

ጋምቤላ ፤መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ብሔራዊ ክብርና አርማ የሆነውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን በድምቀት እንደሚከበር የክልሉ ምክር ቤት አፈ- ጉባኤ ወይዘሮ መሰረት ማቲዎስ ገለጹ።

በጋምቤላ ክልል  የዘንድሮውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን  በተለያዩ ዝግጅቶች  ለማክበር  ዝግጅት ተደርጓል።

የአፈ- ጉባኤዋ ዕለቱን አስመልክተው እንደገለጹት የብሔራዊ ክብርና አርማ የሆነውን የሰንደቅ ዓላማ ቀን ከክልል ደረጃ ጀምሮ እስከ ወረዳ በድምቀት ለማክብር አስፈላጊው ዝግጅት መጠናቀቁን ተናግረዋል።

የሰንደቅ ዓላማ ቀን ከነገ ጥቅምት 1 ቀን 2018 ጀምሮ የህዝቡን በተለይም ወጣቱ የሰንደቅ ዓላማን ምንነት፣ ትርጉምና ክብር በአግባቡ እንዲረዳ በፓናል ውይይትና ሌሎች ዝግጅቶች እንደሚከበር ገልጸዋል።

በጥቅምት 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከጧት 4:30   በጋምቤላ ከተማ አደባባይና በሁሉም የዞንና የወረዳ ከተሞች በተመሳሳይ ስዓት አመራሩ በተገኘበት የሰንደቅ ዓላማ የመስቀል ስነ- ስርዓት ይካሄዳል ብለዋል።

የዘንድሮው የሰንደቅ ዓላማ ቀን እንደ ሀገር በርካታ የልማት ስኬቶችና የማንሰራራት ጅማሮ በተበሰረበት ማግስት የሚከበር መሆኑ ልዩ ትርጉም ያለው መሆኑን አፈ- ጉባኤዋ ገልጸዋል።

 

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም