የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዳዲስ ሹመቶችን ሰጠ - ኢዜአ አማርኛ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዳዲስ ሹመቶችን ሰጠ
አዲስ አበባ፤ መስከረም 14/2018(ኢዜአ)፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዳዲስ ሹመቶችን ሰጥቷል።
በዚህም መሰረት:-
1/ አቶ ሐፍታይ ገብረእግዚያብሔርን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ፤
2/ አቶ ሙሉነህ ደሳለኝ የቄራዎች ድርጅት ስራ አስኪያጅ፤
3/ አቶ ዋለልኝ ደሳለኝን የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት አስተዳደር ባለስልጣን ምክትል ኃላፊ
4/ ወይዘሮ ነስትሆ አብዲ ኮይሬን የኮሪደር እና የወንዝ ዳርቻ ልማት አስተዳደር ባለስልጣን ፅህፈት ቤት ኃላፊ በመሆን መሾማቸውን ኢዜአ ከአስተዳደሩ ያገኘው መረጃ ያመላክታል።