በሻምፒዮንስ ሊጉ ማንችስተር ሲቲ ናፖሊን አሸነፈ - ኢዜአ አማርኛ
በሻምፒዮንስ ሊጉ ማንችስተር ሲቲ ናፖሊን አሸነፈ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 8/2018 (ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ መርሃ ግብር ማንችስተር ሲቲ ናፖሊን 2 ለ 0 አሸንፏል።
ማምሻውን በኢትሃድ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አርሊንግ ሃላንድ በ56ኛው እና ዠረሚ ዶኩ በ65ኛው ደቂቃ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል።
ሃላንድ በሻምፒዮንስ ሊጉ ያስቆጠራቸውን ግቦች ወደ 50 ከፍ አድርጓል።
የተከላካይ ተጫዋቹን ጆቫኒ ዲ ሎሬንዞ በ21ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ያጣው ናፖሊ ከ70 ደቂቃ በላይ በ10 ተጫዋቾች ለመጫወት ተገዷል።
በሌሎች ጨዋታዎች ባርሴሎና በማርከስ ራሽፎርድ ሁለት ግቦች ኒውካስትል ዩናይትድን ከሜዳው ውጪ 2 ለ 1 አሸንፏል።
አንቶኒ ጎርደን ለኒውካስትል ዩናይትድ ብቸኛዋን ጎል አስቆጥሯል።
ኢንትራክት ፍራንክፈርት ጋላታሳራይን 5 ለ 1፣ ስፖርቲንግ ሊዝበን ካይራት አልማቲን 4 ለ 1 አሸንፈዋል።
አስቀድመው ዛሬ በተደረጉ ጨዋታዎች ክለብ ብሩዥ ሞናኮን 4 ለ 1 ሲረታ ኮፐንሃገን ከባየር ሌቨርኩሰን ሁለት አቻ ተለያይተዋል።