በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ መርሃ ግብር ተጠባቂ መርሃ ግብሮች ዛሬ ይካሄዳሉ - ኢዜአ አማርኛ
በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ መርሃ ግብር ተጠባቂ መርሃ ግብሮች ዛሬ ይካሄዳሉ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 8/2018 (ኢዜአ)፦ በ2025/26 የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዛሬ ስድስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።
ማንችስተር ሲቲ ከናፖሊ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በኢትሃድ ስታዲየም የሚያደርጉት ጨዋታ ትኩረትን ስቧል።
ሰማያዊዎቹን ለ10 ዓመታት ያገለገለው ቤልጂየማዊው የአማካይ ተጫዋች ኬቨን ደ ብሮይን የቀድሞ ክለቡን ይገጥማል።
በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ወደ ናፖሊ ያቀናው ደ ብሮይን በኢትሃድ ደማቅ አቀባበል ይደረግለታል ተብሎ ይጠበቃል።
ኒውካስትል ዩናይትድ ከባርሴሎና፣ ኢንትራክት ፍራንክፈርት ከጋላታሳራይ እና ስፖርቲንግ ሊዝበን ከካይራት አልማቲ በተመሳሳይ ምሽት 4 ሰዓት ላይ ይጫወታሉ።
ክለብ ብሩዥ ከሞናኮ እና ኮፐንሃገን ከባየር ሌቨርኩሰን በተመሳሳይ ከምሽቱ 1 ሰዓት ከ45 ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።