የወቅቱ የአውሮፓ ሻምፒዮናስ ሊግ አሸናፊ ፒኤስጂ ከአትላንታ ጋር የመጀመሪያውን ጨዋታ ያደርጋል - ኢዜአ አማርኛ
የወቅቱ የአውሮፓ ሻምፒዮናስ ሊግ አሸናፊ ፒኤስጂ ከአትላንታ ጋር የመጀመሪያውን ጨዋታ ያደርጋል

አዲስ አበባ፤ መስከረም 7/2018(ኢዜአ)፦ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የሁለተኛ ቀን ውሎ ዛሬ ስድስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ።
የወቅቱ የሻምፒዮንስ ሊግ የዋንጫ ባለቤት ፒኤስጂ ምሽት 4 ሰዓት ላይ በፓርክ ደ ፕራንስ አትላንታን ያስተናግዳል።
ሁለቱ ቡድኖች በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ሲገናኙ የአሁኑ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
እ.አ.አ በ2020 በሩብ ፍጻሜው ተገናኝተው ፒኤስጂ 2 ለ 1 በማሸነፍ ለፍጻሜ ማለፉ የሚታወስ ነው።
ፒኤስጂ በጨዋታው ከጣልያኑ ክለብ ጠንካራ ፉክክር ይገጥመዋል ተብሎ ይጠበቃል።
ሊቨርፑል ከአትሌቲኮ ማድሪድ፣ ባየርሙኒክ ከቼልሲ እና አያክስ ከኢንተር ሚላን በተመሳሳይ ከምሽቱ 4 ሰዓት ላይ የሚያደርጓቸው ጨዋታዎች ተጠባቂ ናቸው።
ኦሎምፒያኮስ ከፓፎስ ኤፍሲ እና ስላቪያ ፕራግ ከቦዶ ግሊምት በተመሳሳይ ከምሽቱ 1 ሰዓት ከ45 ላይ ይጫወታሉ።