ቀጥታ፡

ነገ በአዲስ አበባ ለሚካሔደው የድጋፍ ሰልፍ ለትራፊክ ዝግ የሚደረጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ

አዲስ አበባ፤ መስከረም 3/2018(ኢዜአ)፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቆ መመረቁን አስመልክቶ ነገ በመስቀል አደባባይ ለሚደረገው የድጋፍ ሰልፍ የተወሰኑ መንገዶች ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።

በትውልድ ቅብብሎሽ ዕውን የሆነው የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጅማሮ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጳጉሜን 4/2017 ዓ.ም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መመረቁ የሚታወቅ ነው።

ከምረቃው ዕለት ጀምሮ በመላ ሀገሪቱ የተለያዩ ፕሮግራሞች እየተካሄዱ ይገኛሉ።

ነገም በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ የሚካሔደውን ታላቅ የድጋፍ ሰልፍ ተከትሎ ለትራፊክ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን ፖሊስ ይፋ አድርጓል።

በዚህም መሠረት ከመስከረም 3/2018 ዓ.ም ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ የድጋፍ ሰልፉ እስከሚያልቅ ድረስ የሚከተሉት መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ማቆም እንዲሁም እንቅስቃሴ ዝግ ይደረጋሉ፡-

👉ከልደታ ፍርድ ቤት ወደ መስቀል አደባባይ ሜክሲኮ አደባባይ ላይ

👉ከአትላስ ወደ ቅዱስ ዑራኤል ፒኮክ መብራት ላይ

👉ከቡልጋሪያ ወደ ሜክሲኮ ጠማማ ፎቅ ላይ

👉ከቅዱስ ዑራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ባምቢስ መቅረዝ ሆስፒታል መስቀለኛ ላይ )

👉ከኦሎምፒያ አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ (ኦሎምፒያ አደባባይ ላይ)

👉ከብሔራዊ ቤተመንግሥት ወደ መስቀል አደባባይ (ብሔራዊ ቤተመንግሥት ላይ)

👉ከሜትሮሎጂ ወደ ብሔራዊ ቲያትር ጎማ ቁጠባ መብራት ላይ

👉ከተክለ ኃይማኖት አደባባይ በኢምግሬሽን ጥቁር አንበሳ ላይ

👉ከንግድ ማተሚያ ወደ ፍልውሃ ንግድ ማተሚያ መስቀለኛ ላይ

👉ከቸርችል ወደ ጥቁር አንበሳ መብራት ቴዎድሮስ አደባባይ ላይ

👉ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ፓርላማ መብራት

👉ከሀራምቤ መብራት ወደ ሳንጆሴፍ መብራት ሀራምቤ መብራት ላይ

👉ከብሔራዊ ቲያትር ወደ ለገሀር መብራት

👉ከሰንጋ ተራ 40/60 ወደ ለገሃር ሠንጋ ተራ 40/60 መታጠፊያ ላይ

👉ከሜክሲኮ አደባባይ ወደ ሠንጋ ተራ መብራት ሜክሲኮ አደባባይ ላይ

👉ከአረቄ ፋብሪካ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ አረቄ ፋብሪካ መስቀለኛ ላይ

👉ከልደታ ወደ ሜክሲኮ አደባባይ ባልቻ ሆስፒታል መታጠፊያ ላይ

👉ከቫቲካን ኤምባሲ ወደ ሳር ቤት አደባባይ ሳር ቤት አደባባይ ላይ

👉ከቅዱስ ዮሴፍ ወደ መስቀል አደባባይ አጎና ሲኒማ መስቀለኛ ላይ

👉ከቅዱስ ቂርቆስ ታቦት ማደሪያ ወደ ለገሃር ቅዱስ ቂርቆስ ታቦት ማደሪያ መብራት ላይ መንገዶቹ የሚዘጉ ሲሆን በተጠቀሱት መስመሮች ላይ ከዛሬ መስከረም 3 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽት 12፡00 ሠዓት ጀምሮ ተሽከርካሪን አቁሞ መሄድ ፈጽሞ የተከለከለ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አሳስቧል፡፡

#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ #Ethiopia #ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም