በሊጉ የተገናኙት አርባምንጭ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 34ኛ ሳምንት የጨዋታ መርሃ ግብር አርባምንጭ ከተማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ያለ ምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል።

ቀን 9 ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተካሄደው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ግብ ሳያስተናግድ ተጠናቋል።

የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ ስሑል ሽረ እና አዳማ ከተማ ይጫወታሉ።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም