ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ልዩ ቆይታ በክፍል አንድ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች

 

👉ኢትዮጵያዊነት የጋራ እጣ ፈንታ እና ከግል መሻት የተሻገረ ማንነት ነው፤

👉እንደ ህዝብ የምንደርስበትን ግብና መሻት ልናሳካ የምንችለው በዚህ ትልቅ ማንነት ስር ነው፤

👉ኢትዮጵያዊነት ከትናንት እስከ ዛሬ፣ ከዛሬ እስከ ነገ ማዕቀፍ እንጂ ሲመችና ሳይመች የሚለዋወጥ ማንነት አይደለም፤

👉ኢትዮጵያዊነት የማይቆም፣ የነበረ፣ ያለና የሚኖር እንደጅረት የሚፈስ ማንነት ነው፤

👉ኢትዮጵያዊነት የብሄራዊ ጥቅም አካል ነው፤

👉ብሔራዊ ጥቅምን ማሳካት እና ማበልጸግ የሚቻለው ብሄራዊ ትርክት መገንባትና ትውልድ መስራት ሲቻል ነው፤

👉የኢትዮጵያዊነት ማንነት ለሌሎች ማንነት ሁሉ ስር ነው፤ ሁሉም ማንነቶች በኢትዮጵያዊነት ማንነት ስር የሚወድቁ ናቸው

👉ሀገር የቅብብሎሽ ውጤት በመሆኑ ትልውድ እያሰቡ መስራትን ይጠይቃል፤

👉ሀገር ለመገንባት ትናንትን ከዛሬ፤ ዛሬን ከነገ በማስተሳሰር እየሰራን ነው፤

👉ትናንትን በመጠገን ብቻ ነገ አይሰራም፤ የዛሬ ክፍተትን በመፍታት የተሻለ ነገ ለመገንባት እየተሰራ ነው፤

👉የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እና አንድነት ከማንኛውም ኃይል መጠበቅ የሚያስችሉ የጸጥታ እና ደህንነት ተቋማት ተገንብተዋል፤

👉ፈተና እና ስጋት በሰው ውስጥ ያለን እምቅ አቅም ተጠቅሞ ውጤት ማምጣት የሚያስችሉ ጉዳዮች ናቸው፤

👉ሉዓላዊነታችንን በተማሏ ሁኔታ ከማንም ኃይል መጠበቅ እንችላለን፤

👉መንግስት ከፈተናዎች ውስጥ እድልን ፈልቅቆ በማውጣትና በመጠቀም ያከናወናቸው ስራዎች ኢትዮጵያን ተጠቃሚ አድርገዋታል፤

👉ለውጡ በዓለም ላይ ከፍተኛ ድጋፍና ውዳሴ ካስተናገዱ ለውጦች መካከል አንዱ ነው፤

👉መዳረሻችን ብልጽግና፣ የጸናችና ከልመና የተላቀቀች ኢትዮጵያን ማየት ነው፤

👉ውዳሴም እርግማንም ቢመጣ ብዙ ሚዛን የሚያስጥል አልሆነም ሚዛንን ማስጠበቅ የተቻለው መርሃችን መልህቃችን ስለሆነ ነው፤

👉የፖለቲካ ምህዳሩን ለማስፋትና የዴሞክራሲ ባህልን ለማጎልበት የተወሰዱ እርምጃዎች በአብላጫው ውጤት አስገኝተዋል፤

👉 የለውጡ መንግስት የተረከባት ኢትዮጵያ በእዳ የተዘፈቀች፣ በርካታ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ስራ ያቆሙባት፣ የተቋማት ድቀት፣ አሳሪ ሕጎች እና ከፋፋይ ትርክት የነገሰባት ነበረች፤

👉 መዋቅራዊ ችግሮችን ለመፍታት የተወሰዱ እርምጃዎች በአሁኑ ሰዓት የተሻለ ቁመና ያላት ኢትዮጵያ እንድትኖር አስተዋጽኦ አድርጓል፤

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም