በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ዩናይትድ እና በርማውዝ አቻ ተለያዩ - ኢዜአ አማርኛ
በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንችስተር ዩናይትድ እና በርማውዝ አቻ ተለያዩ

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2017(ኢዜአ)፦ በ34ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድ ከሜዳው ውጪ ተጉዞ ከበርንማውዝ ጋር ያደረገውን ጨዋታ አንድ አቻ በሆነ ውጤት አጠናቋል፡፡
የበርንማውዝን ግብ ሴሜኒዮ በመጀመሪያው አጋማሽ ሲያስቆጥር፤ ሆይሉንድ ማንቼስተር ዩናይትድን አቻ ያደረገች ግብ በጨዋታው መጠናቀቂያ አስቆጥሯል፡፡
ውጤቱን ተከትሎ በርንማውዝ በ50 ነጥብ 10ኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ፤ ማንችስተር ዩናይትድ በ39 ነጥብ 14ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
የሊጉ ጨዋታ ሲቀጥል ተጠባቂው የሊቨርፑል እና ቶተንሀም ሆትስፐር ጨዋታ በአንፊልድ ምሽት 12 ሰዓት ከ30 ይደረጋል፡፡
ከጨዋታው አስቀድሞ የሊቨርፑል ደጋፊዎች በአንፊልድ አካባቢ ደማቅ የድጋፍ እንቅስቃሴ እያሳዩ ይገኛሉ፡፡