የኢትዮጵያ መድን እና አዳማ ከተማ ተጠባቂ መርሃ ግብር

አዲስ አበባ ሚያዚያ 8/2017(ኢዜአ):- በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 25 ሳምንት የመጨረሻ ቀን ውሎ የሊጉ መሪ ኢትዮጵያ መድን ከአዳማ ከተማ ጋር ይጫወታል።

የሁለቱ ክለቦች ጨዋታ ከቀኑ 9 ሰዓት በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይካሄዳል።

ኢትዮጵያ መድን 45 ነጥብ የሊጉ አናት ላይ ተቀምጧል። ካሸነፈ ከተከታዩ ኢትዮጵያ ቡና ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ዘጠኝ ከፍ ያደርጋል።

በአንጻሩ 21 ነጥብ 16 ደረጃን ይዞ ወራጅ ቀጠና ውስጥ የሚገኘው አዳማ ከተማ ማሸነፍ ከወራጅነት ቦታ ለመላቀቅ በሚያደርገው ትግል ትርጉም ያለው ሶስት ነጥብ ያስገኝለታል።

25 ሳምንት የመጨረሻ መርሃ ግብር ድሬዳዋ ከተማ እና ኢትዮ ኤሌክትሪክ ምሽት 12 ሰዓት ላይ ያገናኛል።

ድሬዳዋ ከተማ 26 ነጥብ 14 ደረጃን ይዟል። ኢትዮ ኤሌክትሪክ 29 ነጥብ 12 ደረጃ ላይ ይገኛል።

ማሸነፍ ለሁለቱም ቡድኖች ከወራጅ ስጋት ቀጠና ለመራቅ ያግዛቸዋል።

በተያያዘ ዜና ትናንት በተካሄዱ 25 ሳምንት የሶስተኛ ቀን ጨዋታዎች ኢትዮጵያ ቡና ፋሲል ከነማን፣ መቻል አርባምንጭ ከተማን በተመሳሳይ 1 0 አሸንፈዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም