የቶጎ ጫሌ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ዛሬ ይመረቃል - ኢዜአ አማርኛ
የቶጎ ጫሌ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ዛሬ ይመረቃል
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 4/2017 (ኢዜአ)፦የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታዎች አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ (ዶ/ር) ፣ ሡልጣን ወሊ (ዶ/ር ኢ/ር) እና አቶ ሞቱማ መቃሳ የቶጎጫሌ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ለማስመረቅ ጅግጅጋ ገብተዋል።
አመራሮቹ ጅግጅጋ ጋራድ ዊልዋል ኤርፖርት ሲደርሱ የሶማሌ ክልል የውሃና ኢነርጂ ቢሮ አመራሮች አቀባበል እንዳደረጉላቸው የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።