በቦረና ዞን የተገነቡ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ለአገልግሎት በቁ

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 18/2017 (ኢዜአ)፦ በኦሮሚያ ክልል ቦረና ዞን የተገነቡ በፀሐይ ሃይል የሚሰሩ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች አገልግሎት መስጠት ጀምረዋል።

በማስጀመሪያ ስነ ስርዓቱ ላይ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ኢንጂነር ሀብታሙ ኢተፋ (ዶ/ር) ጨምሮ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

በአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት አካል ከሆኑት ፕሮጀክቶች መካከል 100 ኩዩቢክ ሜትር ሪዘርቬየር ያለው የሮምሶ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት ከ106 ሚሊዮን 300 ሺህ ብር በላይ በሚሆን ወጭ ተገንብቶ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።

May be an image of 1 person and text

ፕሮጀክቱ ከአራት ሺህ በላይ የማህበረሰብ ክፍሎችን የመጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንደሚያደርግ እና 27 ሺህ በላይ የሚሆኑ እንስሳቶችን ውሃ እንዲያገኙ የሚያስችል መሆኑን የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።

No photo description available.

የቦረና ዞን ምክትል አስተዳዳሪ አቶ በሪሶ ጋኖ በዞኑ በስድስት ወረዳዎች ተግባራዊ እየተደረገ ያለው ፕሮጀክት ድርቅ ቢከሰት ህብረተሰቡ እንዳይፈናቀልና የተረጋጋ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲኖር አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ሚኒስቴሩ ለፕሮጀክት ግንባታው ላደረገው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

በተያያዘ ዜና በቦረና ዞን ከ131 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እየተገነባ ያለው የዲዳ ያቤሎ የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት እና በዞኑ ከ83 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ውጪ የተገነባው የኤርደር የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክት በቅርቡ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምሩ ተገልጿል።

ሁሉም የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች በሶላር ኢነርጂ እንደሚሰሩ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም