የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ካቀረቧቸው ጥያቄዎች እና አስተያየቶች መካከል:-

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምላሽና ማብራሪያ ቢሰጥባቸው ያሏቸውን ጥያቄዎችና አስተያየቶችን እያቀረቡ ይገኛል፡፡

ከቀረቡት ጥያቄዎች እና አስተያየቶች መካከልም፡-

👉ዘላቂ የሰላም ግንባታን በማጠናከር የሀገሪቱን የልማት ፤የዴሞክራሲ እና አንድነት ከማስቀጠል አንጻር መንግስት ምን እቅድ ይዟል?

👉ታላቁ የህዳሴ ግድብ አካባቢ የሚኖሩ ዜጎች የመብራት አገልግሎት የሚያገኘኙት ከሌላ ቦታ በመሆኑ የመብራት መቆራረጥ በስፋት ይታያል።አካባቢዎቹ መብራት ቀጥታ ከህዳሴ ግድቡ የሚያገኙበት ሁኔታ ቢመቻች፥

👉በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች መንገድን ጨምሮ የተለያዩ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ ምን እየተሰራ ነው?

👉መንግስት ለምርት ዘመኑ የአፈር ማዳበሪያ ለማስገባት እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ የአፈጻጸም ደረጃ ምን ደረጃ ላይ ደርሷል?

👉የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም እና ህዝባዊ ተሳትፎ ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?

👉መንግስት መንገድ እና ኤሌክትሪክ ሃይልን ጨምሮ ፍትሃዊ በሆነ መልኩ መሰረተ ልማትን ተደራሽ ለማድረግ ምን እየሰራ ነው? የሚሉት ይገኙበታል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም