ቀጥታ፡

ባህር ዳር ከተማ ስሑል ሽሬን  በማሸነፍ ደረጃውን ወደ ሶስተኛ ከፍ አድርጓል

አዲስ አበባ፤ ህዳር 17/2017 (ኢዜአ) በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የስምንተኛ ሳምንት ጨዋታ ባህር ዳር ከተማ ስሑል ሽሬን 2 0 አሸንፏል።

ማምሻውን በድሬዳዋ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ አጥቂው ወንደሰን በለጠ 46ኛው እና 84ኛው ደቂቃ የማሸነፊያ ግቦቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል።

ውጤቱን ተከትሎ ባህር ዳር ከተማ  13 ነጥብ ከነበረበት ዘጠነኛ ደረጃ ወደ ሶስተኛ ከፍ ብሏል። በውድድር ዓመቱም አራተኛ ድሉን አስመዝግቧል።


 

በአንጻሩ በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ሽንፈቱን ያስተናገደው ስሑል ሽሬ በሰባት ነጥብ ከነበረበት 15 ደረጃ ወደ 16 ዝቅ ብሎ ወራጅ ቀጠና ውስጥ ይገኛል።

ቀን ላይ በተካሄደ ጨዋታ ወላይታ ድቻ እና ፋሲል ከነማ አንድ አቻ ተለያይተዋል።

ጨዋታዎቹን ተከትሎ የስምንተኛ ሳምንት መርሃ ግብር ተጠናቋል።

የዘጠነኛ ሳምንት ጨዋታዎች ከሕዳር 19 ቀን 2017 . እንደሚካሄዱ የሊጉ አክሲዮን ማህበር አስታውቋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም