አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ - ኢዜአ አማርኛ
አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ፤መስከረም 27/2017 (ኢዜአ) ፡- አምባሳደር ታዬ አፅቀስላሴ የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል።
የኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሆነው የተሾሙት አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ቃለ-መሐላ ፈጽመዋል።
6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን የመክፈቻ ሥነ-ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።
አምባሳደር ታዬ የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሆነው ከመሾማቸው በፊትም የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ፡፡