የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዳዲስ ሹመቶችን ሲሰጥ ሽግሽግ በማድረግ ከኃላፊነትም አንስቷል - ኢዜአ አማርኛ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዳዲስ ሹመቶችን ሲሰጥ ሽግሽግ በማድረግ ከኃላፊነትም አንስቷል

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 16/2016(ኢዜአ):-የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዳዲስ ሹመቶችን ሲሰጥ ሽግሽግ በማድረግ ከኃላፊነትም ማንሳቱን አስታወቀ::
የከተማ አስተዳደሩ በ2016 ዓ. ም. ባደረገው የስራ አፈፃፀም ግምገማ የተገኙ ውጤታማ ጥንካሬዎችን በማላቅ የተለዩ ድክመቶችን በማረም ላይ ይገኛል::
የተጀመረውን የተቋማት ግንባታና የሪፎርም ስራዎችን አጠናክሮ ለማስቀጠል አዳዲስ ሹመቶችን ሰጥቷል ፣ ሽግሽግ አድርጓል እንዲሁም የተወሰኑትን ከኃላፊነት አንስቷል::
በዚህም መሰረት:-
1. አቶ አብርሃም ታደሰ - የከንቲባ የአደረጃጀት አማካሪ
2.. አቶ ይመር ከበደ- የመንግስት ልማት ድርጅቶች ባለስልጣን ሃላፊ
በከተማ ማዕከል ደረጃ የተሰጡ ሹመቶች:-
1. አቶ አደም ኑሪ - የፕላንና ልማት ቢሮ ሃላፊ
2. አቶ ቢኒያም ምክሩ - የገቢዎቸ ቢሮ ሃላፊ
3. ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ- የንግድ ቢሮ ሃላፊ
4. ዶ/ር ዳዲ ወዳጆ - የከንቲባ ስትራቴጂክ ጉዳዮች አማካሪ
5. አቶ ተስፋዬ ደንድር - የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ምክትል ቢሮ ሃላፊ
6. አቶ ማቆያ አለማየሁ - የግንባታና ዲዛይን ምክትል ቢሮ ሃላፊ
7. አቶ አስመሮም ብርሃኔ - የትራንስፖርት ምክትል ቢሮ ሃላፊ
8. አቶ ተስፋዬ ጫኔ - የሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ምክትል ቢሮ ሃላፊ
9. አቶ ዩኑስ አደም - የመሬት ልማትና አስተዳደር ምክትል ቢሮ ሃላፊ
10. አቶ አዳነ ሱሌ - የገቢዎች ቢሮ ፅ/ ቤት ሃላፊ
11. ወ/ሮ ወርቅነሽ ሰቦቃ - የገቢዎች ምክትል ቢሮ ሃላፊ
12. አቶ ዘገየ በላይነህ - የፀረ-ሙሰና ኮሚሽን ምክትል ሃላፊ
13. ወ/ሮ ፀሀይ ኪባሞ - የበጎ ፈቃድና ህዝብ ተሳትፎ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር
14. ኮ/ር አህመድ ሙሃመድ - የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ሃላፊ
15. አቶ ከፍያለው ታደሰ- የደንብ ማስከበር ባለስልጣን ምክትል ሃላፊ
16. አቶ ዘመኑ ታደሰ - የመብራት አገልግሎት ፅ/ ቤት ሃላፊ
17. ወ/ሮ ወይንሸት ብዛኔ - የከንቲባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ምክትል ሃላፊ
18. አቶ አሰፋ ቶላ - የዲዛይንና ግንባታ ማማከር ፅ/ቤት ሃላፊ
በክፍለ ከተማ ደረጃ
1. ወ/ ሮ ካባ መብራቱ - የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ
2. ወ/ሮ አበባ እሸቴ - የልደታ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ
3. አቶ ጌታሁን አበራ - የአራዳ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ
4. አቶ መብራቱ ደሴ የንፋስ ስልክ ላፍቶ ፓርቲ ፅ/ ቤት ሃላፊ በመሆን ተሹመዋል::