የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ ከአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት አባላት ጋር ተወያዩ - ኢዜአ አማርኛ
የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ ከአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት አባላት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 10/2016(ኢዜአ)፦የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) በኢትዮጵያ ከአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት አባላት ጋር ተወያይተዋል።
በውይይቱም በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ጨምሮ በኢትዮጵያ የአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት አባላት ተሳትፈዋል።
በዚሁ ጊዜ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ መንግሥት ተግባራዊ ያደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ እና ስትራተጂክ ጉዳዮች ላይ ገለፃ አድርገዋል።
ውይይቱ በኢትዮጵያ የአሜሪካ የንግድ ምክር ቤት አባላት ከኢትዮጵያ አቻዎቻቸው ጋር መስተጋብር እንዲፈጥሩ ያስቻለ መሆኑም ተገልጿል።