የኢትዮጵያ አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ማምሻውን ይደረጋሉ - ኢዜአ አማርኛ
የኢትዮጵያ አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ማምሻውን ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 4/2016(ኢዜአ)፦ በ33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች የኢትዮጵያ አትሌቶች የሚሳተፉባቸው ሁለት የፍጻሜ ውድድሮች ከጥቂት ቆይታ በኋላ ይካሄዳሉ።
ከምሽቱ 2 ሰዓት ከ50 ደቂቃ ላይ በወንዶች 5000 ሜትር ፍጻሜ አትሌት ሐጎስ ገብረሕይወት፣ አትሌት ቢኒያም መሐሪና አትሌት አዲሱ ይሁኔ ይወዳደራሉ።
አትሌት ጉዳፍ ፀጋይና አትሌት ድርቢ ወልተጂ የሚሳተፉበት የ15000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ ከምሽቱ 3 ሰዓት ከ15 ደቂቃ ላይ ይደረጋል።
ኢትዮጵያ በፓሪስ እየተካሄደ ባለው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ ዛሬ በወንዶች ማራቶን በአትሌት ታምራት ቶላ ማግኘቷ ይታወቃል።