አትሌት ታምራት ቶላ የመጀመሪያውን የኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኘ - ኢዜአ አማርኛ
አትሌት ታምራት ቶላ የመጀመሪያውን የኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ አስገኘ
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 4/2016(ኢዜአ)፦በ33ኛው የኦሊምፒክ ጨዋታዎች በወንዶች ማራቶን የፍጻሜ ውድድር አትሌት ታምራት ቶላ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የወርቅ ሜዳሊያ አስገኝቷል።
ታምራት 2 ሰዓት ከ6 ደቂቃ ከ26 ሴኮንድ በርቀቱ የኦሊምፒክ ክብረ ወሰንን አሻሽሏል።
አትሌት ደሬሳ ገለታ አምስተኛና አንጋፋው አትሌት ቀነኒሳ በቀለ 39ኛ ደረጃን ይዘው አጠናቀዋል።