የጨልጨል መስኖ ልማት ፕሮጀክት በ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ግንባታው በመካሄድ ላይ ይገኛል - ኢዜአ አማርኛ
የጨልጨል መስኖ ልማት ፕሮጀክት በ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ግንባታው በመካሄድ ላይ ይገኛል
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2016(ኢዜአ)፦ የጨልጨል መስኖ ልማት ፕሮጀክት በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ ባሌ ዞን ራይቱ እና ጊኒር ወረዳዎች መካከል በ5 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ግንባታው በመካሄድ ላይ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
የፕሮጀክቱ ግንባታ ሲጠናቀቅ 4 ሺህ 145 ሔክታር መሬት በመስኖ በማልማት ከዘጠኝ ሺህ በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ተገልጿል፡፡
ፕሮጀክቱ በታህሳስ 2012 ዓ/ም የተጀመረ ሲሆን በ2018 በጀት ዓመት መጨረሻ ለማጠናቀቅ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን ከመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡