መረጃዎችን ለመሰበሰብ የሚረዳ "ሃይ አልቲትዩድ ሳተላይት ባሉን" ወደ አየር ተለቀቀ - ኢዜአ አማርኛ
መረጃዎችን ለመሰበሰብ የሚረዳ "ሃይ አልቲትዩድ ሳተላይት ባሉን" ወደ አየር ተለቀቀ
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 3/2016(ኢዜአ)፦ የስፔስ ሳይንስና ጂኦ ስፓሻል ኢኒስቲትዩት መረጃን ለመሰብሰብ የሚረዳ "ሃይ አልቲትዩድ ሳተላይት ባሉን " ወደ አየር ለቀቀ ።
ሳተላይት ባሉንን የመልቀቅ ስነ ስርአት በሸገር ከተማ ሱሉሉታ ክፍለ ከተማ የተካሄደ ሲሆን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ዴኤታ ይሽሩን ዓለማሁ (ዶ/ር)፣ የቦይንግ ኩባንያ የአፍሪካ ዳይሬክተር አምባሳደር ሄኖክ ተፈራ እንዲሁም ተማሪዎች ተገኝተዋል ፡፡
ኢኒስቲትዩቱ ከቦይንግ እና ፋሴሳ ከተሰኙ ድርጅቶች ጋር በመተባበር "ፓዝ ወይ ቱ ስፔስ' በሚል መሪ ሃሳብ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎች በማስመረቅ ላይ ነው፡፡
ተማሪዎቹ ከ 16 እስከ 20 ዓመት ዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሲሆን "ሃይ አልቲትዩድ ሳተላይት ባሉን " ዲዛይንና ግንባታ ዙሪያ ለአምስት ወራት ስልጠና የወሰዱ ናቸው፡፡
ተማሪዎቹ በስልጠናው የቀሰሙትን እውቀት ተጠቅመው የሰሩትን ሃይ አልቲትዩድ ሳተላይት ባሉን የሙከራ ውጤት አቅርበዋል፡፡