ቀጥታ፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ 8 ተደለደለች

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 27/2016(ኢዜአ፦ኢትዮጵያ በሞሮኮ አስተናጋጅነት በሚካሄደው 35ኛ የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ በምድብ 8 ከጊኒ፣ታንዛንያና ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ተደልድላለች።

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን(ካፍ) የ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ድልድል የዕጣ ማውጣት ስነ ስርዓት ዛሬ በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ አድርጓል።


 

በዚሁ መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በምድብ 8 ከጊኒ፣ታንዛንያና ዴሞክራሲ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጋር ተደልድላለች።

በአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ 48 አገራት በ12 ምድብ ተከፍለው ጨዋታቸውን ያደርጋሉ።

የማጣሪያ ጨዋታዎች በመስከረም ወር 2017 ዓ.ም ይጀምራሉ።

በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ 24 አገራት ይሳተፋሉ።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም