በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው የምክክር ምዕራፍ የተሳተፉ አካላት እነማን ናቸው? - ኢዜአ አማርኛ
በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው የምክክር ምዕራፍ የተሳተፉ አካላት እነማን ናቸው?
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 29/2016(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ ባካሄደው የአጀንዳ ልየታ ምክክር ምዕራፍ የሚከተሉት አካላት ተሳትፈዋል።
እነሱም፦
121 የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍል ተወካዮች
228 የተቋማት እና የማህበራት ተወካዮች
52 የፖለቲካ ፓርቲ ተወካዮች
128 የመንግስት አካላት ተወካዮች
100 ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች
16 የፓለቲካ ፓርቲዎች
11 ሞደሬተሮች (ውይይቶቹን በማስተባበር) ተሳትፈዋል።
እነዚህ ባለድርሻ አካላት በቡድን የተወያዩባቸውን አጀንዳዎች ግንቦት 26/2016 ዓ.ም ለተወካዮቻቸው ሰጥተዋል፡፡
በሂደቱ ሁሉም ተወካዮች በሞደሬተሮች አጋዥነት አጀንዳዎችን አደራጅተዋል፡፡
ግንቦት 27/ 2016 ዓ.ም የአምስቱ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች አጀንዳቸውን ለኮሚሽኑ ማቅረባቸውንም የሃገራዊ ምክክር ኮሚሽን መረጃ ያሳያል።