ኢትዮጵያ ሌሴቶን 2 ለ 1 አሸነፈች - ኢዜአ አማርኛ
ኢትዮጵያ ሌሴቶን 2 ለ 1 አሸነፈች
295
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 15/2016(ኢዜአ)፦ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የአቋም መፈተሻ ጨዋታ ኢትዮጵያ ሌሴቶን 2 ለ 1 አሸንፋለች፡፡
ጎሎቹን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ቸርነት ጉግሳ እና ከነዓን ማርክነህ ከእረፍት መልስ አስቆጥረዋል፡፡
ለሌሴቶ ብቸኛዋን ግብ ሌህሎሆኖሎ ፎቶአኔ ማስቆጠሩን ከኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የተገኘው መረጃ ያመላክታል፡፡