ተቋርጦ የቆየው የኢትየጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ይጀመራል

አዲስ አበባ ፤ ህዳር 20 /2016 (ኢዜአ) በአለም አቀፍ ውድድሮች ምክንያት ባለፉት 27 ቀናት ተቋርጦ የቆየው የኢትየጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጀመራል፡፡

ዛሬ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ድሬዳዋ ከነማ  ከወላይታ  ዲቻ ፤ ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት  አምበሪቾ ዱራሚ ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ሊጉ ነገም ቀጥሎ የሚውል ሲሆን ዘጠኝ ሰዓት ኢትዮጵያ መድህን ከመቻል ፤ በአስራ ሁለት ሰዓት ሻሸመኔ ከተማ ከወልቂጤ ከተማ የሚጫወቱ ይሆናል።

 ጨዋታዎቹ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይካሄዳሉ፡፡ 

ሊጉን ቅዱስ ጊዮርጊስ በ13 ነጥብ ሲመራ  ሻሸመኔ ከነማ  በአንድ ነጥብ የሊጉ መጨረሻ ላይ ተቀምጧል፡።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም