ተቋርጦ የቆየው የኢትየጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ይጀመራል - ኢዜአ አማርኛ
ተቋርጦ የቆየው የኢትየጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ይጀመራል
![](/documents/42135/0/%E1%8D%90%E1%88%AC+%284%29.jpg/25aa9749-2c6f-2b8c-fceb-782b1092d164?version=1.0&t=1701325333360&download=true)
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 20 /2016 (ኢዜአ) በአለም አቀፍ ውድድሮች ምክንያት ባለፉት 27 ቀናት ተቋርጦ የቆየው የኢትየጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በሚደረጉ ሁለት ጨዋታዎች ይጀመራል፡፡
ዛሬ ከቀኑ ዘጠኝ ሰዓት ድሬዳዋ ከነማ ከወላይታ ዲቻ ፤ ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት አምበሪቾ ዱራሚ ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ሊጉ ነገም ቀጥሎ የሚውል ሲሆን ዘጠኝ ሰዓት ኢትዮጵያ መድህን ከመቻል ፤ በአስራ ሁለት ሰዓት ሻሸመኔ ከተማ ከወልቂጤ ከተማ የሚጫወቱ ይሆናል።
ጨዋታዎቹ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይካሄዳሉ፡፡
ሊጉን ቅዱስ ጊዮርጊስ በ13 ነጥብ ሲመራ ሻሸመኔ ከነማ በአንድ ነጥብ የሊጉ መጨረሻ ላይ ተቀምጧል፡።