አንጎላ ከኢትዮጵያ ጋር በግብርናው ዘርፍ በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ፕሬዝዳንት ጆአዎ ማኑዌል ጎንካልቬስ ሎሬንኮ ገለጹ - ኢዜአ አማርኛ
አንጎላ ከኢትዮጵያ ጋር በግብርናው ዘርፍ በትብብር መስራት እንደምትፈልግ ፕሬዝዳንት ጆአዎ ማኑዌል ጎንካልቬስ ሎሬንኮ ገለጹ
አዲስ አበባ ፤ ህዳር 18/2016 (ኢዜአ) ፡-አንጎላ ከኢትዮጵያ ጋር በግብርናው ዘርፍ በትብብር መስራት እንደምትፈልግ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ጆአዎ ማኑዌል ጎንካልቬስ ሎሬንኮ ገለጹ።
አምባሳደር ፍርቱና ዲበኮ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአንጎላ ሪፐብሊክ ፕሬዝዳንት ጆአዎ ማኑዌል ጎንካልቬስ ሎሬንኮ አቅርበዋል ።
በስነ ስርዓቱ ላይ ኢትዮጵያ በንግድ ፣በግብርና በቱሪዝም እና በኢንቨስትመንት ዘርፎች ከአንጎላ ሪፐብሊክ ጋር በቅርበት መስራት እንደምትፈልግ አምባሳደር ፍርቱና ለፕሬዝዳንቱ ገልፀዋል ።
ፕሬዝዳንቱ በበኩላቸው ኢትዮጵያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በግብርናው ዘርፍ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበች እንደምትገኝ ገልፀው፤ በትብብር መስራት እንደሚፈልጉ መግለፃቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያመለክታል።