የግብርና ሚኒስትሩና   የሲዳማ ክልል አመራሮች   ችግኞችን  ተንከባከቡ 

አዲስ አበባ ፤ኅዳር 16/ 2016/ (ኢዜአ)፦ የግብርና ሚኒስትሩና የሲዳማ ክልል ከፍተኛ አመራሮች በአዋሳ  የታቦር ተራራ   ላይ የተተከሉ ችግኞችን ተንከባከቡ ፡፡

የግብርና ሚኒስትሩ ግርማ አመንቴ (ዶ/ር)  በወቅቱ እንዳሉት  ለአረንጓዴ አሻራ የተጣለውን ግብ  ለማሳካት በክረምት ወቅት  የተተከሉ ችግኞችን ጽድቀት በቅርበት መከታተልና መንከባከብ ይገባል ።



 ማህበረሰቡም ሆነ ተቋማት በክረምት ወቅት  የተከሏቸውን ችግኞች የመንከባከብና ውሃ የማጠጣት ስራ አጠናክረው መቀጠል ይኖርበቸዋል ነው ያሉት ።

ሚኒስትሩ   በሲዳማ ክልል በሚኖራቸው ቆይታ  በእንስሳትና ዓሳ ሀብት ልማት ፕሮጀክት (LFSDP) ድጋፍ የተከናወኑና ሌሎች ልማት ስራዎችን  እንደሚጎበኙ  ከግብርና ሚኒስቴር ማህበራዊ ገጽ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም