ቀጥታ፡

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የተለያዩ የአመራር ሹመቶችን ሰጠ

አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 25/2015(ኢዜአ)፦የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት በ13/12/2015 ዓ.ም በተካሄደው የክልሉ ምስረታ ጉባኤ ከክልሉ ሕዝብ ምክር ቤት በተሰጠው ውክልና መሰረት የካቢኔ አባላትን ሹመት ሰጥቷል።

በዚህም መሰረት:-

1 አቶ አክሊሉ ለማ - የትራንስፖርት እና መንገድ ልማት ቢሮ ኃላፊ

2 አቶ ቢረጋ ብርሃኑ - የኢንተርፕራይዝ ልማትና ሥራ ፅ/ፈ/ ቢሮ ኃላፊ

3 ወ/ሮ ካሰች ኤልያስ - የሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ

4 ዶ/ር እንዳልካቸው ጌታቸው - ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ

5 ዶ/ር ቦጋለ ቦሼ - የፕላን ቢሮ ኃላፊ

6 አቶ ብርሃኑ ዘውዴ - የከተማና እና መሠረተ ልማት ቢሮ ኃላፊ

7 ወ/ሮ አለምነሽ ደመቀ - የገቢዎች ቢሮ ኃላፊ

8 አቶ ግዛቴ ጊጄ - የደንና አካባቢ ጥበቃ ልማት ቢሮ ኃላፊ

9 ዶ/ር ዋኖ ዋሎሌ - የሠራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ

10 አቶ ሀ/ማሪያም ተስፋዬ - የግብርና ቢሮ ኃላፊ

11 አቶ አብዩት ደምሴ - የቴክኒካና ሙያ ትምህርት ሥልጠና ቢሮ ኃላፊ

12 አቶ ተፈሪ አባተ - የፋይናንስ ቢሮ ኃላፊ

13 አቶ ታረቀኝ ሀብቴ - የመስኖና ቆላማ አከባቢ ልማት ቢሮ ኃላፊ

14 አቶ ንጋቱ ዳንሳ - የፐቢሊክ ሠርቪስ እና ሰዉ ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊ

15 አቶ ተካልኝ ጋሎ - ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ

16 አቶ አቤነዘር ተረፈ - የፍትህ ቢሮ ኃላፊ

17 አቶ ገለቦ ጎልቶሞ - የንግድና ገበያ ልማት ቢሮ ኃላፊ

18 ዶ/ር ኦንጋዬ ኦዳ - የኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊ

19 ወ/ሮ ሰናይት ሰለሞን - የመንግሥት ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ

20 አቶ አርሻሎ አርካል - የወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ

21 ወ/ሪት ፍሬህይወት ዱባለ - የባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ

22 አቶ እንዳሻው ሽብሩ - የጤና ቢሮ ኃላፊ

23 አቶ ወገኔ ብዙነህ - የሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሆነው ተሹመዋል።

ሆነው መሾማቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም