የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን /ኢቢሲ/ "በዘመን ጅረት" በሚል ያዘጋጀውን የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ ተከፈተ - ኢዜአ አማርኛ
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን /ኢቢሲ/ "በዘመን ጅረት" በሚል ያዘጋጀውን የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕይ ተከፈተ
አዲስ አበባ ሰኔ 26/2015(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን /ኢቢሲ/ አዲስ ባስገነባው የሚዲያ ኮምፕሌክስ "በዘመን ጅረት" በሚል ያዘጋጀውን የፎቶ ግራፍ አውደ- ርዕይ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ከፍተውታል።
አውደ- ርዕዩ ኢቢሲ በቴሌቭዥንና በሬዲዮ ቴክኖሎጂ ያለፈባቸውንና አሁን ያለበትን የስራ ዕንቅስቃሴ የሚያሳይ ነው።
አፈ- ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር ከተለያዩ የአገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን የስራ ሀላፊዎች ጋር በመሆን አውደ-ርዕዩን ጎብኝተውታል።
የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዋና ስራ አስፈጻሚ ሰይፈ ደርቤን ጨምሮ የኦቢኤን፣ ዋልታና ሌሎች የሚዲያ ከፍተኛ ሀላፊዎች በመርሀ ግብሩ ላይ ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን እያስገነባ ያለውን የሚዲያ ኮምፕሌክስ 5 የቲቪና 3 የሬዲዮ እስቲዲዮ፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳና ሌሎች አገልግሎት የሚሰጡ ቦታዎችን በውስጡ ይዟል።
የኢቢሲ የሚዲያ ኮምፕሌክስ ግንባታው ከአንድ አመት በፊት የተጀመረ ሲሆን ከነገ ወዲያ ረቡዕ ይመረቃል ተብሏል።