ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከብራዚሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር እንደሚወያዩ ገለጹ - ኢዜአ አማርኛ
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከብራዚሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር እንደሚወያዩ ገለጹ

አዲስ አበባ ግንቦት 28/2015(ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ከብራዚሉ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ ጋር በኢትዮጵያ እና በብራዚል መካከል ግንኙነትን ስለማጠናከር እና በብዝኃ ወገን ጉዳዮች ላይ እንደሚወያዩ አስታወቁ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት “ከብራዚል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማውሮ ቪዬራ ጋር ዛሬ ተገናኝተናል” ብለዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በመልዕክታቸው “በኢትዮጵያ እና በብራዚል መካከል ግንኙነትን ስለማጠናከር እና በብዝኃ ወገን ጉዳዮች ላይ ውይይት እናደርጋለን” ሲሉም ገልጸዋል።