ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በነገው ዕለት የመንግስትን የስድስት ወር ሪፖርት ለምክር ቤቱ ያቀርባሉ

229

አዲስ አበባ መጋቢት 18/2015 (ኢዜአ)፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በነገው ዕለት የመንግስትን የስድስት ወር አፈጻጸም ሪፖርት ለኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያቀርባሉ፡፡

ምክር ቤቱ ነገ በሚያካሂደው 11ኛ መደበኛ ስብሰባው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ የሚቀርበውን ሪፖርት ያዳምጣል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከምክር ቤቱ አባላት ለሚነሱ የተለያዩ ወቅታዊና ሀገራዊ ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም