ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድርን አትሌት መዲና ኢሳ በአንደኝነት አጠናቀቀች

አዲስ አበባ መጋቢት 17/2015 (ኢዜአ) የሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 . ሩጫ ውድድርአትሌት መዲና ኢሳ በአንደኝነት አጠናቀቀች


 

አትሌት መዲና ኢሳ በመሪነት በማጠናቀቋ 70ሺህ ብር ተሸላሚ ስትሆን በተጨማሪም በውድድሩ አዲስ ክብረ-ወሰን በማስመዝገቧ የ50ሺህ ብር ሽልማት ተበርክቶላታል።

በውድድሩ አትሌት ፅጌ ገብረ ሰላማ 2ኛ እንዲሁም አትሌት መልክናት ውዱ 3ኛ ደረጃን ይዘው በማጠናቀቃቸው እንደቅደም ተከተላቸው 45ሺህ ብር እና የ30ሺህ ብር ተሸላሚ ሆነዋል

በውድድሩ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ፣ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ፣ ሻለቃ አትሌት ሀይሌ ገብረ ሥላሴ፣ አትሌት መሰረት ደፋር፣ አትሌት ለተሰንበት ግደይን ጨምሮ የተለያዩ አትሌቶችና እንግዶች ተገኝተዋል።

2015 ሳፋሪኮም ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪሎሜትር ሩጫቦታዬ፤ መብቴ፤ ድምፄበሚል መሪ ቃል እየተካሄደ ባለው በዚህ ውድድር አትሌቶች፣ 15 ሺህ የጤና ሯጮች፤ እንዲሁም አምባሳደሮች እየተሳተፉ ነው።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም