የረመዳን ጾም የፊታችን ሐሙስ ይጀመራል

558

አዲስ አበባ መጋቢት 12/2015(ኢዜአ):- የ1444ኛው ዓመተ ሒጅራ የረመዳን ጾም የፊታችን ሐሙስ እንደሚጀመር የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አስታወቀ።

ጾሙ ሐሙስ የሚጀመረው የረመዳን ወር ጨረቃ ዛሬ(ማክሰኞ) ባለመታየቷ እንደሆነም ገልጿል።

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ጾሙ ለመላው ሙስሊም ማህበረሰብ የአንድነት፣በጎ ነገር የማድረግ፣የመተዛዘንና የበረከት እንዲሆን ምኞታቸውን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት
2015
ዓ.ም